| 18.03.2010 | 14:00 UTC
ዋሽንግተን፡ የዩኤስ እና የእስራኤል ግንኙነት
በእስራኤልና በዩኤስ አሜሪካ መካከል ሰሞኑን አንዳንድ የሀሳብ ልዩነት ቢፈጠርም ከእስራኤል ጋር ያለው የሀገራቸው ግንኙነት ቀውስ ውስጥ እንደማይገኝ የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ አረጋገጡ። ዋሽንግተን ወደፊትም የዩኤስ አሜሪካ ዋነኛ ተጓዳኝ ሆና እንደምትቆይ ኦባማ አስታውቀዋል።
« ተመልከት፡ እስራኤል ከቅርብ ተጓዳኞቻችን መካከል አንድዋ ናት፡ እና እኛ እና የእስራኤል ህዝብ ሊቋረጥ የማይችል ልዩ ግንኙነት አለን። ነገር ግን አንዳንዴ ጓደኞች ላይስማሙ ይችላሉ። እና ምክትል ፕሬዚደንት ባይድንን ወደ እስራኤል የላኩት ይህንኑ የድጋፍ መልዕክት ለማጉላት እና የእስራኤል ጸጥታ ደህንነትም በፍጹም ሊጣስ እንደማይገባ ያለኝን እምነት ለማረጋገጥ ነው። ብዙ የምንጋራቸው የጋራ ጥቅሞችም አሉን። »
ይሁንና፡ የእስራኤል መንግስት በአከራካሪው የምስራቅ ኢየሩሳሌም ለአይሁዳይውያን አዳዲስ መኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት መወሰኑ በመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ለማውረድ የተጀመረውን ጥረት እንደማይጠቅም ኦባማ ከማስታወቅ አልተቆጠቡም። እስራኤል 1.600 መኖሪያ ቤቶችን የመገንባት ዕቅድ አውጥታለች።










